መልአከ ሕይወት ሆይ፣ የሰውነቴኝ አካላት በጉልምስና ግቢ!
- ለሰው ልጆች ጉልምስናን ብርታትንም ከምትሰጣቸው ከመልአከ ሕይወት ጋራ አምስተኛው ሰላምታ ነው።
- እነሆ፣ ሰሙስ የተጠራ ካልሆነ፣ እንግዲህ ሻማው ታማኝ ነበልባል እንዴት ሊሰጥ ይችላልን?
- ስለዚህ ወደሚበቅሉ አትክልት ውጣ፣ ለመልካም በቀል ጎልማሳ ይህን ቃል ተናገር፦ ፈጣሪው ለፈጠረው ጥሩ ሕያው ተክል፣ ክብር ይሁንህ። [በወንዲዳድ 19:18]
- ያንጊዜ በአንተና በወንድምህ በዛፉ መካከል የሕይወት ወንዝ ይፈስሳልና የሰውነት ጤና፣ የእግር ፍጥነት፣ የዦሮ ማዳመጥ፣ የክንድ ብርታት፣ የንሥርም ዓይን ብርሃን ለአንተ ይሆኑሃል። [በያሽት 16:13]
- ከመልአከ ሕይወት፣ ከምድራዊት እማማ ቅድስት መልዕክተኛ ጋራ ያለው ሰላምታ እንዲህ ነው። ሥላህ።